Psalms 92

ጻድቅ ሰው ሲደሰት

በሰንበት ቀን የሚዘመር መዝሙር፤ ማሕሌት።

1 እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው፤
ልዑል ሆይ፤ ለስምህ መዘመር ጥሩ ነው፤
2ምሕረትህን በማለዳ፣
ታማኝነትህንም በሌሊት ማወጅ መልካም ነው፤
3ዐሥር አውታር ባለው በገና፣
በመሰንቆም ቅኝት ታጅቦ ማወጅ ጥሩ ነው።

4 እግዚአብሔር ሆይ፤ በሥራህ ስለ ተደሰትሁ፣
ስለ እጅህ ሥራ በደስታ እዘምራለሁ።
5 እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህ እንዴት ታላቅ ነው!
ሐሳብህስ ምን ያህል ጥልቅ ነው!
6ደነዝ ሰው ይህን አያውቅም፤
ነኁላላም አያስተውለውም።
7ክፉዎች እንደ ሣር ቢበቅሉ፣
ክፉ አድራጊዎች ቢለመልሙ፣
ለዘላለሙ ይጠፋሉ፤
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ለዘላለም ልዑል ነህ።

9ጠላቶችህ እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ ይጠፋሉና፤
ክፉ አድራጊዎችም ሁሉ ይበተናሉ።
10የእኔን ቀንድ ግን እንደ አውራሪስ ቀንድ
ጥንካሬን የሚያመለክት ነው።
ከፍ ከፍ አደረግኸው፤
በለጋ ዘይትም አረሰረስኸኝ።
11ዐይኖቼ የባላንጦቼን ውድቀት አዩ፤
ጆሮዎቼም የክፉ ጠላቶቼን ድቅቀት ሰሙ።

12ጻድቃን እንደ ዘንባባ ይንሰራፋሉ፤
እንደ ሊባኖስ ዝግባም ይንዠረገጋሉ።
13 በእግዚአብሔር ቤት ተተክለዋል፤
በአምላካችንም አደባባይ ይንሰራፋሉ።
14ባረጁ ጊዜ እንኳ ያፈራሉ፤
እንደ ለመለሙና እንደ ጠነከሩም ይኖራሉ።
15እግዚአብሔር ትክክለኛ ነው፤
እርሱ ዐለቴ ነው፤ በእርሱ ዘንድ እንከን የለም” ይላሉ።
Copyright information for AmhNASV