Psalms 131

በእግዚአብሔር መታመን

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።

1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ልቤ አልታበየም፤
ዐይኔ ከፍ ከፍ አላለም፤
ሐሳቤ ለዐጕል ትልቅነት አልተነሣሣም፤
ከዐቅሜም በላይ አልተንጠራራሁም።
2ነገር ግን ነፍሴን ጸጥ፣ ዝም አሰኘኋት፤
ጡት የጣለ ልጅ ዐርፎ እናቱ ላይ እንደሚቀመጥ፣
ነፍሴ ጡት እንዳስተዉት ሕፃን በውስጤ ጸጥ አለች።

3እስራኤል ሆይ፤ ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣
በእግዚአብሔር ተስፋ አድርግ።
Copyright information for AmhNASV