Psalms 127

በእግዚአብሔር መታመን

የሰሎሞን መዝሙረ መዓርግ


1 እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፣
ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤
እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፣
ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።

2 የዕለት ጒርስ ለማግኘት በመጣር፣
ማልዳችሁ መነሣታችሁ፣
አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው፤
እርሱ ለሚወዳቸው እንቅልፍን ያድላልና።
ወይም ተኝተው ሳሉ ምግብ ያዘጋጅላቸዋል።


3 እነሆ፤ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፤
የማሕፀንም ፍሬ ከቸርነቱ የሚገኝ ነው።

4 በወጣትነት የተገኙ ወንዶች ልጆች፣
በጦረኛ እጅ እንዳሉ ፍላጾች ናቸው።

5 ኰረጆዎቹ በእነዚህ የተሞሉ፣
የተባረከ ሰው ነው፤
ከጠላቶቻቸው ጋር በአደባባይ በሚሟ
ገቱበት ጊዜ፣ አይዋረዱም።
Copyright information for AmhNASV